Wednesday, April 11, 2012

የቴዲ አፍሮን ሙዚቃ ለሞባይል ጥሪ ድምፅ 100 ሺሕ ተጠቃሚዎች ገዙት:: “ኃይል” በሚለው ዘፈን ላይ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅን “ፈራን” ግጥሙን በማንበብ ተሳትፎበታል፡፡


በመጪው ቅዳሜ የሚለቀቀው የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) “ጥቁር ሰውአልበም ማስተዋወቂያ የሆነው አፍሪካየተባለው የሞባይል ጥሪ ድምፅ (Ringtone) 100 ሺሕ ኮፒ ለተጠቃሚዎች ተሸጠ፡፡

Michael Hailu: The talent behind Teddy Afro
በአዲካ ኮምዩኒኬሽንና ኢቨንትስ፣ በቤሌማ ኢንተርቴመንትና 4 አፍሪ ትብብር ለአንድ ሚሊዮን የሞባይል ተጠቃሚዎች የአጭር የስልክ መልዕክት ተልኮ፣ እስካሁን የጥሪ ድምፁን 100 ሺሕ ሰዎች መግዛታቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ምንጮች አክለው እንደገለጹትም፣ በሚመጡት ቀናት ተጨማሪ ስድስት የቴዲ ዘፈኖች ለሞባይል የስልክ ጥሪ እንዲያገለግሉ 11 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች በአጭር የስልክ መልዕክት ጥሪ ይተላለፋሉ፡፡

አፍሪካየሚለው ዘፈን በአቡጊዳ ባንድ መቀናበሩ ታውቋል፡፡ በሞባይል ስልኩ ጥሪውን ለመጫን የሚፈልግ ማንም ሰው በአጭር የስልክ መልዕክቱ ጥሪ ሲቀርብለት ከተስማማ ሁለት ብር ይቆረጥበታል፡፡ ይህ የስልክ መጥርያ ማስታወቂያ (Ringtone Promotion) አዲስ የሆነ የማስተዋወቂያ ዘዴ መሆኑን የገለጸው አዲካ፣ ሌሎች ዘፈኖቹን በዚህ መንገድ እንደሚያስተዋውቅ ገልጿል፡፡ የቴዲ አፍሮ ዘፈን በዚህ የማስተዋወቅ ዘዴ ለሚሊዮኖች ተልኮ በሺዎች የሚቆጠሩት ሲገዙት ይህ ለመጀመርያ ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡ 

በጥቀር ሰውአልበም ውስጥ አሥራ አንድ ዘፈኖች የተካተቱ ሲሆን፣ ዘጠኝ ዘፈኖችን ያቀናበረው ወጣቱ ሙዚቀኛ ሚካኤል ኃይሉ ነው፡፡ የአልበሙ መጠርያ የሆነውንጥቁር ሰውያቀናበረው ታዋቂው አቀናባሪ አበጋዝ ክብረ ወርቅ ሺዎታ ነው፡፡

የአልበሙን ሙሉ ግጥምና ዜማ የደረሰው ራሱ ቴዲ አፍሮ ሲሆን፣ ለየት ባለ ሁኔታም የታዋቂው ገጣሚና የቴአትር ጸሐፊ የሟቹ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅንም ድምፅ ተካቶበታል፡፡ኃይልበሚለው ዘፈን ላይ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅንፈራንየሚል መጠርያ ያለውን ግጥሙን በማንበብ ተሳትፎበታል፡፡

አልበሙም ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ ለአዲስ አበባና ለክልል አድማጮች በኤሌክትራ ሙዚቃ ቤትና በአምባሰል ሙዚቃ ቤት አማካይነት የሚሰራጭ ሲሆን፣ ለሰሜን ኢትዮጵያ አድማጮች ደግሞ በጣና ኢንተርቴይመንት በኩል ይሰራጫል፡፡
ይህን አልበም ፕሮዲዩስ ያደረገው፣ እያሰራጨና እያስተዋወቀ ያለው አዲካ ኮሙኒኬሽንና ኢቨንትስ ከቤሌማ ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ሲሆን፣ ብቸኛ ስፖንሰሩም ሜታ ቢራ ነው፡፡

ቴዲ አፍሮጥቁር ሰውለተባለው አልበሙ 4.6 ሚሊዮን ብር እንደተከፈለው ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ቢገለጽም፣ አዲካ ግን የገንዘቡን መጠን ለመግለጽ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ይህ ክፍያ በተለያዩ አካላት የተለያዩ መጠኖች ቢገለጽም፣ ትክክለኛውን ክፍያ ለማወቅ ፈጽሞ አልተቻለም፡፡
http://www.ethiopianreporter.com

No comments:

Post a Comment